የይዘት ማውጫ
አጭር መግለጫ
ይህ መመርያ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች የበላይ ኮሚሽነር ( United Nations High Commissioner for Refugees (ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር-UNHCR) አንድ ግለሰብ ስደተኛ መሆኑንና አለመሆኑን የሚለይበት መንገድ ነው። ይህም የስደተኛ መለያ ውሳኔ (refugee status determination-አር-ኤስ-ዲ-RSD) በመባል ይታወቃል።
ባሉበት አገር ውስጥ የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) መስርያ ቤት እንደ ስደተኛ እንዲያውቆት ማመልከቻ ካቀረቡ፤ የአር-ኤስ-ዲ (RSD)ቃለመጠይቅ ሊደረግሎት ይችላል። የአር-ኤስ-ዲ (RSD) ቃለመጠይቅ በ ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) መስርያ ቤት በዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን የሚደረግ ቃለመጠይቅ ነው። ይሄው ባለስልጣንም በዓለም ዓቀፍ ህግ መሰረት፡ የስደተኛ መስፈርቶችን የሚያሟሉና የማያሟሉ መሆንዎን ይወስናል።
የስደተኛ መብት ለማግኘት ማመልከቻ የሚያስገባው ማነው?
በአንድ ቤተሰብ ውስጥ አንድ ግለሰብ ቀዳማይ (ዋነኛው) አመልካች (primary applicant (ፒ-ኤ-PA) ይሆናል። ይህንን አመልካች ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) እንደ ስደተኛ ሲቀበለው፤ ባለቤቱንና 18 ዓመት ዕድሜ ያልሞላቸው ልጆቹንም በሙሉ እንደ ስደተኛ ያውቃቸዋል።
ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR)፤ የእርሶ ጥገኞች የሆኑትን ሌሎችንም በፋይሎ ውስጥ ሊያስገባቸው ይችላል። ለምሳሌ ራሳቸውን በራሳቸው ሊረዱ የማይችሉ፣ ከእርሶ ጋር የሚቀመጡና በዕድሜ የገፉ ወላጆችዎን እንደ ጥገኞች ሊቆጥራቸው ይችላል። ማንም ጥገኛ የሆነ ሰው ደግሞ የስደተኛ መስፈርቶችን እስካሟላ ድረስ እንደ ስደተኛ ሊቆጠር ይችላል።
ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ከ18 ዓመት በላይ ዕድሜ ያላቸውን በሙሉ አንድ በአንድ በተናጠል ቃለመጠይቅ እንደሚያደርግላቸው ማወቅ ያስፈልጋል። ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ልጆችንም ቃለመጠይቅ ሊያደርግ ይችላል፡ ለልጆች ቃለመጠይቅ የሚያደርጉ ግን ልጆችን ልዩ ትምህርት ያላቸው የ ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣናት ብቻ ናቸው።
የስደተኛ መለያ ውሳኔ (አር-ኤስ-ዲ (RSD) ቃለመጠይቅ ዓላማ ምንድነው? ስደተኛ ሲባል ምን ማለት እንደሆነ የሚያስረዳ
በአር-ኤስ-ዲ (RSD) ቃለመጠይቅ፤ ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) የስደተኛ መስፈርቶችን የሚያሟሉ ወይም የማያሟሉ መሆንዎን ይወስናል። አንድ ሰው እንደ ስደተኛ ለመቆጠር የሚከተሉትን ማሟላት አለበት፤
- ከአገሮ ውጭ መሆን አለቦት
- ወደ አገሮ ቢመለሱ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስቦት እንደሚችል ስጋት አሎት። እዚህ ላይ፤ ወደ አገሮ ቢመለሱ ምን ጉዳት ሊደርስቦት እንደሚችል በዝርዝር ማስረዳት ያስፈልጎታል።
- ያሎት ስጋት “ጥሩ መሰረት” ያለው መሆን አለበት። አገሬ ውስጥ ከፍተኛ ስቃይና ጉዳት ይደርስብኛል የሚል ስጋት ለምን እንዳደረቦት ማስረዳት አለቦት። ይህ የሚሰማዎት ፍርሃት ቀደም ሲል በላዮ ላይ በደረሰቦት ግፍ ምክንያት ከሆነ በደንብ ያስረዱ፤ ከእርሶ ጋር ተመሳሳይ ጉዳይ ያላቸው ሰዎች ግፍ እንደተፈጸመባቸው ያስረዱ። ከራሶ ንግግር ውጪ፤ ማረጋገጫ ማምጣት አለቦት ባይባሉም፤ ማረጋገጫ ወረቀቶችን ወይም ምስክሮችን ማቅረብ ጉዳዮን ሊያግዝ እንደሚችል ይረዱ። ማረጋገጫዎች ሊሆኑ የሚችሉ የሚከተሉት ናቸው፡
- በጽሁፍ የተሰጦት ዛቻ ወይም ማስፈራርያ ወረቀት ወይም በአካሎ ላይ የደረሰ ጉዳት የሚያሳይ ሰዕል
- ወታደር-ነክ ዶኩመንቶች፣ በውትድርና ውስጥ ገብተው ከነበረ፣ ያገለገሉበት ወረቀት ለምሳሌ ወታደራዊ ጽሁፍ ወይም ካርድ፤ በውትድርና ገብተው ያገለገሉ ግን አሁን ይህንን የሚያረጋገጥ ማረጋገጫ ከሌሎት፤ ለምን ምንም ዓይነት ማስረጃ እንደሌሎት ለማስረዳት ተዘጋጁ።
- ከስደተኛ ጥያቄዎ ጋር የተያየዙ የሕክምና ወይም የጤና ዶኩመንቶች ካሎት
- የቤተሰብ መጻህፍት፤ የልጆችዎ የልደት ምስክር ወረቀት፤ የጋብቻ ወይም የፍቺ ዶኩመንቶች
- በአገሮ መንግስት ጉዳት እንደሚደርስቦት ወይም መንግስት ጉዳት ሊያደርሱቦት ከሚችሉ ሌሎች ሰዎች ሊጠብቆት የማይችል ወይም የማይፈልግ መሆኑን የሚያስረዳ ጽሁፍ.
- በእነዚህ በሚከተሉት ምክንያቶች በላዬ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊደርስብኝ ይችላል የሚል ፍርሃት አለኝ፡ :
- በዘር
- በሃይማኖት
- በብሔር
- በፖለቲካ አስተያየት
- በልዩ ማህበራዊ ቡድን አባል መሆን
ልዩ ማህበራዊ ቡድን (particular social group) ሲባል አንድ ሊለውጡት ወይም ሊቀይሩት የማይችሉ ተመሳሳይ ነገር ያላቸው ሰዎች የታቀፉበት ቡድን ማለት ነው። ለምሳሌ አንድ ሰው የአንድ የመንግስት ተቃዋሚ የቤተሰብ አባል በመሆኑ ጉዳት ይደርስብኝ ይሆናል ብሎ መፍራት ወይም የኤል-ጂ-ቢ-ቲ-አይ( LGBTI) አባል ከሆነ ጉዳት ሊደርስብኝ ይችላል ብሎ መፍራትን ያካትታል።
ግን ጉዳት ይደርስብኝ ይሆናል የሚል ፍራቻ መኖር ብቻ በቂ አይደለም። ጉዳት ሊደርስቦት የሚችለው ከእነዚህ ከሚከተሉት ምክንያቶች ውስጥ አንዱ ሊደርስቦት እንደሚችል ማሳየት ወይም ማረጋገጥ ያስፈልጎታል፡
- አገሮ ውስጥ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ መንቀሳቀስ የማይችሉ ከሆነ
- ለስደተኞች ከሚሰጥ የስደተኛ ጥበቃ የተገለሉ መሆን የለቦትም። እነኚህ የሚገለሉት ደግሞ፤
- ከፍተኛ ወንጄል የፈጸሙ ወይም በጦርነት ግዜ በሰላማዊ ህዝብ ላይ ወንጄል የፈጸሙ አመልካቾች
- ከሌላ አገር የዜግነት ወረቀት ያገኙ ወይም የዜግነት ወረቀት የመሰለ ይሰጦታል ተብለው በሌላ አገር ቃል የተገባላቸው አመልካቾች።
ከቃለመጠይቁ በፊት መደረግ የሚገባው ዝግጅት
ወደ ቃለመጠይቁ ከመግባትዎ በፊት፤ በህይወትዎ ስላጋጠሞት ነገሮች በቅደም ተከተል በአጭሩ በጽሁፍ ይያዙ። ይህም የሚከተሉትን ሊያጠቃልል ይችላል፤ ከአገሮ በመጨረሻ የወጡበት ዕለት ወይም ዛቻ የቀረበቦት ዕለት የመሳሰሉትን ሊያጠቃልል ይችላል። እነኚህ ሁኔታዎች አንዳንዴ የማይፈለጉ ወይም መጥፎ ትዝታዎችን ሊቀሰቅሱ ይችላሉ። ግን ስለነኝህ ጉዳዮች ለመናገር ዝግጁ መሆን በጣም አስፈላጊ ነው።
መጻፍ የማይችሉ ከሆነ፤ እርዳታ መጠየቅ ይችላሉ ወይም ወረቀት ላይ ሳያሰፍሩት በቃሎ ብቻ መከለስ ይችላሉ።
የጻፉትን ወደ ቃለመጠይቁ ሲመጡ ይዘውት አይምጡ። ጽሁፉ እንድትዘጋጁ የሚያግዞት ብቻ ነው።
በቃለመጠይቁ ወቅት ታሪኮን ስለመናገር
በቃለመጠይቁ ወቅት ሁሌም እውነቱን ተናገሩ። ዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) እርሶ ተፈጸመ ብለው የተናገሩት ሁሉ ሃቅነት እንዳለውና እንደሌለው ሁሌም ያረጋግጣል። ይህም ማለት እርሶ የተናገሩት ሁሉ እውነት ነውን ብለው በመወሰን ላይ መሆናቸውን ይገልጻል ማለት ነው።
የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን አገሮ ውስጥ ያጋጠሞትን ሁሉ እንዲናገሩ ይጠይቆታል። ከአገሮ ለምን እንደወጡም ይጠየቃሉ።
በፊት እንደዚህ ሆነ በኋላ ደግሞ ይህ ሆነ እያሉ ቅደም ተከተል በመጠበቅ ታሪኮን በዝርዝር ቢያቀርቡ፤ የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን ምን እንዳጋጠሞት በደንብ እንዲያውቅ ይረዳዋል።
የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን፤ እርሶ የተናገሩትን ሁሉ፤ በአገሮ ውስጥ ስላለው ሁኔታ ከዜና ማሰራጫዎችም ሆነ ከሌሎች ከተገኘው መረጃ ጋር ያወዳድራል።
የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን፤ ስለተመዘገቡበት ፎርም አንስቶ በወቅቱ እርሶ የሰጡትን መረጃ በቃለመጠይቁ ወቅት ከተናገሩት ጋር ያመዛዝናል። የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣን እርሶ በመመዝገብያው ፎርም የተናገሩትን በቃለመጠይቁ ከተናገሩት ጋር በማወዳደር በሁለቱ መካከል ለምን ልዩነት እንደሚታይ ይጠይቆታል። የሚታየው ልዩነት ለምን እንደሆነ ወይም በሁለቱ መካከል ምንም ልዩነት እንደሌለና ሁለቱ መረጃዎች አንድ ዓይነት መሆናቸውን ማስረዳት አለቦት።
ቤተሰቦችዎ ከእርሶ ጋር እያሉ፤ በእነሱ ፊት መግለጽ የማይፈልጉት ነገር ካለ፤ እነሱ እያሉ የግድ መግለጽ አለቦት አይባሉም። ግን ታሪኮን በግልጽ መናገር ያስፈልጎታል። የቤተሰቦ አባላት በሌሉብት ቃለመጠይቁን መቀጠል እንደሚፈልጉ ለዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር ( UNHCR) ባለስልጣን መግለጽ አለቦት።
ታሪኮን በዝርዝር ስለመናገር
በላዮ ላይ ጉዳት ማን እንደፈጸመና ሊጎዳዎት እንደሞከረ በግልጽ ለይተው ይናገሩ። ለምሳሌ፤ በቦታው ምን ያህል ሰዎች እንደነበሩ፣ የለበሱት ልብስ ምን ዓይነት እንደነበር፣ ራሳቸውን አስተዋወቁን? እርሶ በበኩልዎ እነማን ነበሩ ይላሉ?
ይህ ጉዳይ ምን ያህል ግዜ በተደጋጋሚ እንደተደረገ በትክክል ይወቁ። ለምሳሌ አንዴ ብቻ ነው? አንዴ ካልሆነ ስንት ግዜ ተደጋገመ? እና መቼ ነው ጉዳዩ የተፈጸመው?
የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር ( UNHCR) ባለስልጣን የሚጠይቃቸውን ጥያቄዎች ሁሉ በጥሞና አዳምጡ። መልስ ሲሰጡ ሃቀኛ ሁኑ፤ በግልጽም ተናገሩ። ለተጠየቁት ጥያቄ ትክክለኛውን መልስ መስጠቶን ያስተውሉ።
ከአስተርጓሚ ጋር መስራት
ለቃለመጠየቁ አስተርጓሚ እንዲደረግሎት ከጠየቁ፤ ለሚጠየቁት ጥያቄዎች መልስ ሲሰጡ አጠር አጠር አድረገው ይመልሱ። ይህም አስተጓሚው ታሪኮን በሙሉ በደንብ አድረጎ እንዲተርጉም ያግዘዋል። አስተርጓሚው የሚናገሩትን ታሪክ ለባለስልጣኑ ሲተረጉም በትክክልና በዝርዝር በደንብ እንዲተረጉም በቂ ግዜ ስጡት።
የሚከተሉትን የመሳሰሉ ችግሮች ካጋጠሞት፡ ለባለስልጣኑ ይንገሩ፡
- አስተርጓሚውን በደንብ የመረዳት ችግር ካለቦት
- ተርጓሚው ምናልባት አልተረዳኝም ይሆናል የሚል ስጋት ካደረቦት
- አስተርጓሚው ያሉትን ሁሉ በትክክል ወይም ሙሉ በሙሉ አይተረጉምም የሚሉ ከሆነ
- አስተርጓሚው ለእኔ ምንም ከበሬታ የለውም የሚል ቅሬታ ካሎት
ከዛ በኋላ የአስተርጓሚ ችግር እንዳለቦት በዝርዝር አስረዱ። አስተርጓሚው በጉዳዮ የመጨረሻ ውሳኔ ላይ ምንም ተጽእኖ አይኖረውም። ከቃለመጠየቁ በኋላ፤ አስተርጓሚው ለምንም ዓይነት ውይይት ጉዳዮን አያነሳም።በአጠቃላይም አስተርጓሚዎች በቃለመጠይቁ የሰሙትን ሁሉ በሚስጢር እንድይዙ ይጠየቃሉ።
የቃለመጠይቅ ሚስጢራዊነት
በቃለመጠቁ መጀመርያ ላይ የቤተሰቦችዎ አባላት በሙሉ መገኘት ሊኖርባቸው ይችል ይሆናል። በቤተሰቦችዎ ፊት መናገር የማይፈልጉት ጥያቄም ሊጠየቁ ይችላሉ። ጉዳዩን ሳይገልጹ ከመቅረት ይልቅ ስለዚህ ጉዳይ ከባለስልጣን ጋር ብቻ በሚስጢር መናገር እፈልጋለሁ ብለው ለባለስልጣኑ ይግለጹ። ይህም አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን ከማስቀረት ወይም “አላውቅም” የሚል መልስ ከመስጠት የተሻለ ነው።
አጠቃላይ መረጃ
- የተጠየቁትን ጥያቄ መልስ ሳያውቁ ሲቀሩ ምን መልስ መስጠት እንዳለቦት፡ አንድ ጥያቄ ሲጠየቁ መልሱን የማያውቁት ከሆነ፤ ዝም ብለው በተሳሳተ መረጃ የተሳሳተ መልስ ለመስጠት አይሞክሩ፡
- የአንድ ነገር ዝርዝር መረጃን ማስታወስ ካልቻሉ፤ እስከሚያውቁት ድረስ ይግለጹ። ከዛ በኋላ ዝርዝር መግለጫውን ለምን እንደረሱ ምክንያቱን ይግለጹ። ሁሌም ቢሆን አላስታውስም ወይም ስለዚህ ጉዳይ አላውቅም ማለትና ለምን እንደማያውቁ ማስረዳት የተሻለ ነው።
- ለምሳሌ አንድ ነገር የተፈጸመበትን ቀን እንዲገልጹ ሲጠየቁ፤ እርሶ የሚያስታውሱት በ 2013 በጋ ወራት ላይ መሆኑን ብቻ ከሆነ፤ የተሳሳተ ቀን ከመስጠት ይልቅ በደፈናው 2013 በጋ ወራት ማለት ይሻላል።
- እረፍት ካስፈለጎት የእረፍት ግዜ እንዲሰጦት መጠየቅ ይችላሉ። በቃለመጠይቁ ወቅት የእረፍት ግዜ እንዲሰጦት መጠየቅ ነውር አይደለም። ታሪኮን በሙሉ በሚናገሩበት ወቅት፤ ምቾት እንዲሰማዎት አስፈላጊ ነው። ትንሽ አለመረጋጋት ወይም ብስጭት ከተሰማዎት፤ እንዲረጋጉና ሃሳቦን እንዲያሰባስቡ አጭር የእረፍት ግዜ እንዲሰጦት ይጠይቁ።
- ምንም ነገር አይተው፤ ሁሉንም ተናገሩ፡ ለተጠየቁት ጥያቄ ሁሉ ያሎትን መልስ ለባለስልጣኑ መግለጾን ያረጋግጡ። ባለሰልጣኑ ያቀረባቸውን ጥያቄዎች በሙሉ ይመልሱ፣ ባለስልጣኑ በጠየቃቸው ጥያቄዎች ላይ ያተኩሩ።
- ሁሌም ሃቀኛ ይሁኑ፡ ምንም ዓይነት ጥያቄ ሲጠየቁ፣ ሁሌም እውነቱን ይናገሩ። የምሰጠው መልስ ጉዳዬን ሊጎዳው ይችል ይሆናል ብለው ከፈሩ፤ ሁሌም እውነቱን መናገር የተሻለ ነው። ከዛ በኋላ ይህ ጉዳይ ጉዳዮን ለምን ሊጎዳ እንደማይገባው በዝርዝር ያስረዱ። የሃሰት መረጃ ከሰጡ ግን ባለስልጣኑ ጉዳዮን ውድቅ ሊያደርግ ይችላል። ።
ከአር-ኤስ-ዲ (RSD) ቃለመጠይቅ በኋላ
ከቃለመጠይቆ በኋላ፣ ወድያውኑ በቃለመጠይቆ ወቅት የተናገሩትን ቁልፍ የሆኑ ጉዳዮችን ዝርዝር በጽሑፍ ያስፍሩ። ቃለመጠይቅ ያደረጎለትን የዩ-ኤን-ኤች-ሲ-አር (UNHCR) ባለስልጣንና የአስተርጓሚውን ስም ይጻፉ። በቃለመጠይቁ ወቅት ያደረጉት ንግግር ምናልባት ቃመጠይቅ ያደረገሎትን ሰው ሊያደናግር ይችል ይሆናል የሚሉትን ወደያዉኑ ይጻፉት።
የአለም አቀፍ የስደተኞች እርዳታ ፕሮጀክት (IRAP) ለአንዳንድ ስደተኞች እና ተፈናቃዮች ነፃ የህግ እርዳታ ይሰጣል።
- IRAP አንዳንድ ሰዎች አገልግሎት እንዲያገኙ እና የስደተኛ እና የቪዛ ማመልከቻዎችን እንዲያዘጋጁ ይረዳቸዋል።
- IRAP የየትኛውም መንግስት፣ IOM ወይም UNHCR አካል አይደለም።
- IRAP የስደተኛ ደረጃ ወይም ቪዛ ሊሰጥ ወይም ጉዳዮችን ማፋጠን አይችልም።
- IRAP የገንዘብ ድጋፍ መስጠት፣ መኖሪያ ቤት ማግኘት ወይም መክፈል፣ ወይም ሥራ ማግኘት አይችልም።
- ሁሉም የ IRAP እርዳታ ነፃ ነው። ማንም ሰው ከIRAP ጋር ግንኙነት ያለው ገንዘብ ወይም ሌላ አገልግሎት ሊጠይቅዎት መብት የለውም።
IRAP ሰዎችን በፍላጎታቸው እና ለስደት ሁኔታ ብቁነታቸውን መሰረት አድርጎ ለመርዳት ይወስናል። IRAP በማንኛውም ሌላ ማህበራዊ ወይም ፖለቲካዊ ወይም ሃይማኖታዊ መመዘኛዎች ሰዎችን ለመርዳት አይወስንም።
ይህ ድህረ ገጽ ለአንዳንድ ስደተኞች ስለሚገኙ የህግ ሂደቶች አጠቃላይ መረጃ ይሰጣል። ለግል ማመልከቻዎች እንደ ህጋዊ ምክር አይደለም።
መስፈርቶች ሊለወጡ ይችላሉ። ጥያቄዎን ሲወስኑ ሁል ጊዜ ከመንግስት ወይም ከኤጀንሲው ወቅታዊ መስፈርቶችን ያረጋግጡ።
በስደተኞች ድንገተኛ አደጋ ውስጥ ከሆኑ፣ በሚኖሩበት አገር ያለውን የ UNHCR ቢሮ እንዲያነጋግሩ እንመክራለን።
Comments
0 comments
Please sign in to leave a comment.